ከ10-13 ሳምንታት መካከል ያለ እርግዝናዎችም ደህንነቱ በተጠበቀና ውጤታማ በሆነ ሁኔታ በውርጃ ክኒኖች ሊቋረጥ ይችላል፣ ነገር ግን ከግምት ውስጥ መግባት ያለባቸው ኣንዳንድ እሳቤዎች ኣሉ።
በእርግዝና መጀመሪያ ኣካባቢ የሚከሰቱ ውርጃዎች ኣነስተኛ የመወሳሰብ ኣደጋ ኣላቸው። እርግዝናው ማደጉ በቀጠለ ቁጥር የመወሳሰብ ኣደጋው እየጨመረ ይሄዳል። ከታች ያለው ቻርት እንዴት የመወሳሰብ ኣደጋ ከእርግዝና ቆይታ ጋር እንደሚጨምር ያሳያል። በኋለኛ እርግዝናዎች ውስጥ ኣደጋ ቢጨምርም በ13 ሳምንታት የሚደረግ ውርጃ ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ ይታሰባል።
ህክምናዊ ውርጃ ሴቶች እንዲደሙ ያረጋል። ይህ ደም መፍሰስ ከተለመደው የወር ኣበባሽ ሊበዛ ይችላል እና የረጋ ደም ሊኖረው ይችላል። ከ10-11 የእርግዝና ሳምንታት መካከል ያሉ ሴቶች ሊታወቅ የሚችል ነገር ሊያዩ ይችላሉ ወይም ስጋ ሊመስል ይችላል። ይህ የተለመደ ነው እና ሊያስደነግጥሽ ኣይገባም። ውርጃው እንደተጠበቀው የመቀጠሉ ምልክት ነው። እንደ ከባድ የወር ኣበባ ትልልቅ የረጉ ደሞችን ወይም ስጋን ወደ ሽንት ቤት መጣል ነው። ውርጃ ህገ-ወጥ በሆነበት ኣገር የምትኖሪ ከሆነ ሊታወቅ የሚችል ነገርን ሁሉ በጥንቃቄና በሚስጥር ኣስወግጂ።
ይህ ድር ጣቢያ በአግባቡ መስራት እንዲችል ስም-አልባ ኩኪዎች እና የተለያዩ የሶስተኛ ወገን አገልግሎቶች ሊያስፈልገው ይችላል። የእኛን ደንቦችና ሁኔታዎች እና የግላዊነት መመሪያዎች ማንበብ ይችላሉ። ይህን ጣቢያ መጠቀሙን በመቀጠልዎ እኛ ይህን እንድናደርግ ፈቃድዎን እየሰጡን ነው።'